የብጹዕ #አቡነ ፋኑኤል ጥፋት ምኑ ላይ ነው?

ከ85ቱ የሐዋርያት ቀኖና መሐል #40ኛው እንዲህ ይላል ፡-

“ጳጳስ (ለግል ጉዳዩ ካስፈለገው) ንብረት ሃብት ይኑረው:: የግል ንብረቱ በግልጽ ለሕዝብ ይታወቅ፡፡ የቤተ ክርስቲያኑም ንብረት ከጳጳሱ ንብረት ተለይቶ ለሕዝብ ይገለጽ፡፡ ጳጳስ ሲሞት ንብረቱን ለፈለገው የመስጠት የማውረስ መብት ስለ አለው ነው፡፡ ከቤተ ክርስቲያን ንብረት ጋር እንዳይቀላቀልና የቤተ ክርስቲያን ንብረት በማስመሰል የግል ገንዘቡ እንዳይወሰድና የመውረስ መብት ያላቸው ሚስትና ልጆች ወይም የቅርብ ዘመዶች፣ የወንድ አሽከር፣ የቤት ገረድ ተገቢ ድርሻቸውን እንዳያጡ፡፡ ስለዚህ እግዚአብሔር ባወቀ ገንዘብ የቤተ ክርስቲያኑም ያለአግባብ እንዳይባክን፣ የጳጳሱም ለተገቢው ባለመብት እንዲደርስ፣ በገንዘቡ የተነሣ ሰዎች እርስ በራሳቸው እንዳይጋጩና ሙት ወቃሽ ሁኔታ እንዳይፈጠር ተገቢ ነው፡፡”

ከዚህ አንጻር ብጹዕ አቡነ ፋኑኤል በስማቸው ተመዝግቦ የነበረውን ቤታቸውን #ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል በስጦታ ማበርከታቸው  ጥፋቱ ምኑ ላይ ነው? እስቲ ያልተረዳነው ወይም ያላየነው ነገር ካለ አስረዱን፡፡

Leave a Reply