እንኳን በሰላምና በጤና ለብርሃነ መስቀሉ አደረሰን! አደረሳችሁ!

ባይ ባይ ኢ-አማኒው  አሥር አለቃ ፋንታሁን ሙጬ!!!

የዘንድሮው የደመራ በዓል አከባበር ሀገራችንና ወገኖቻችን በጣም በከባድና በአሳዛኝ ሁኔታ ላይ ሁነው ብናከብርም ዳሩ #በመስቀል አደባባይ እጅግ ደስ የሚል የበረከት በዓል አክብረናል፡፡ ብዙዎቻችን ከረካንበት ነገር አንዱ በዘንድሮው የመስቀል ደመራ በዓል ላይ ከ the…the…the…is… is…was…ነጻ የሆነ ተገቢው የሆነ የመድረክ መሪ አግኝተን እነ ሙጬን ከመሳሰሉ ደፋሮች ተላቀን በተገቢው ቦታ ተገቢውን ሰው በማየታችን ነው፡፡

ከመስቀል ደመራ በዓል አከባበር ጋር በተያያዘ በአማኙም ይሁን በኢ-አማንያን ዘንድ ተደጋግሞ ከሚሰነዘሩ ትችቶች አንዱ ምነው ቤተክርስቲያኒቱ ሰው የላትም እንዴ? ምነው ሌላው ቢቀር present, past and future tense ለይቶ በማይናገር ሰው መድረኩን የምትጫወቱበት ይባል ነበር፡፡

ዘንድሮ እግዚአብሔር ይመስገን መድረኩ ለሚገባ ሰው በመሰጠቱ መምህራችን ቀሲስ ዳንኤል ይደልዎ! ብለናል፡፡ ለዚህ ትልቁን ድርሻ የተወጡት አድርባይነት የሌለባቸው ባሕታዊና የልማት አባት የሆኑት ብጹዕ አቡነ ያሬድ የጠቅላይ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጅ እንደሚሆኑ ጥርጥር የለንም፡፡ ምክንያቱም ልክ ወደ ኃላፊነት እንደመጡ የመጀመሪያ ሥራ ያደረጉት ለረጅም አመታት አንደ መዥገር ተጣብቆ ሲጫወትበት ከኖረበት የሰበካ ኩባኤ ማደራጃ መመሪያ ኃላፊነት በማስወገድ ነው፡፡ በዚህም ከአድርባይነት የጸዱ እውነተኛ የቤተክርስቲያኒቱ አባት መሆናቸውን በተግባር አስመስክረዋል፡፡

በምትኩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የውጪ ግንኙነት የበላይ ኃላፊ፣ የነገረ መለኮት ሊቅ፣ መምህር፣ ተመራማሪ፣የሃይማኖት፣ የታሪክ፣ የባህልና የሥነ ጥበብ ባለሙያና ፀሐፊ የሆኑት የቤተክርስቲያናችን ዕንቁ ልጅ ለሆኑት ለመምህር ቀሲስ ዳንኤል ሰይፈሚካኤል መስጠቱ ይበል ያሰኛል፡፡ ቅድስት ቤተክርስቲያን ብዙ ጊዜ የምትሰደበው እነ ሙጬ የመሳሰሉ መንገደኛና የምንግዜም ደም መጣጭ ሰዎች ሳይገባቸው ቦታ ይዘው ነው፡፡ ይህ የማስተካከያ እርምጃ በሌሎችም ዘርፎች እንደሚቀጥሉ ተስፋ አለን!!!

ባይ ባይ ኢ-አማኒው  አሥር አለቃ ፋንታሁን ሙጬ!!!

መልካም በዓል!

ይቆየን  

Leave a comment